Telegram Group & Telegram Channel
ጥያቄ:- ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት ነው? ለምን  ይሰገዳል?

መልስ

ታቦት በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በምህረት በሚገለጥበት ጊዜ ዙፋኑ ነው፡፡  ከክርስትና በፊት የብሉይ ኪዳን አገር የነበረችው ኢትዮጵያ በክርስትና ጊዜም ከብሉይ ኪዳንም ያገኘቻቸውን ጠቃሚ ነገሮች በክርስትና መንፈስ እየተረጎመች ትጠቀምባቸዋለች፡፡
ከብሉይ ኪዳን የወሰደቻቸው አንዱ ጽላተ ኪዳን ታቦተ ህጉ ነው፡፡ የደብተራ ኦሪት ጽላት እግዚአብሔር በደመና ተከናንቦ ሙሴንና አሮንን የሚነጋግርበት ለእስራኤል ልጆችም በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ታቦት ግን የአምላክ ስጋና ደም የሚፈተትበት ስጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ህይወት አለው፡፡ ስጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን ሁሉ የሚጠራበት የምህረት ምስዋዕ ነው፡፡ ክብርና ሰግደትም ለዚህ ይደረግለታል፡፡

👉 በርግጥ የሐዲስ ኪዳን ታቦት ከብሉይ ኪዳን ታቦት የሚለይበት መንገድ አለው። በሐዲስ ኪዳን ታቦት የሚባለው የብሉይን ታቦትና ጽላት አንድ አድርጎ የያዘ ይመስላል። በብሉይ ጽላት ላይ  የተጻፉት ቃላትም አልተጻፉበትም። ምክንያቱም በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ቀዳማዊ እንደተገለጸው ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ የሚችል ጻሕልና ጽዋ የሚያስቀምጥ እንዲሆን ተወስኗል። በላዩም አልፋ ወኦ፤ ቤጣ ፤ የውጣ የሚባሉ አስማተ መለኮት (የአምላክ ስሞች) በአራቱ ማዕዘን ይቀረጽበታል። በመካከል ሥነ ስቅለት ይቀረጽበታል። "ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ታቦተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ተብሎ ይጻፍበታል። ኪሩቤል መንበረ ጸባዖትን እንደተሸከሙ ይሳልበታል። ከዚያም የቅዱሱ ስም ይቀረጽበታል። እስከ 15ኛው ምእተ ዓመት ከላይ ቅድስት ሥላሴ
ዝቅ ብሎ እመቤታችን ወደ ላይ አንገቷን በማቅናት ከታች ደግሞ ቅዱሱን ወደ እመቤታችን አቅንተው ይቀረጹ ነበር። ከላይ ታቦቱ ጻሕል ጽዋ እንዲያስቀምጥ ሆኖ የሚሰራው መሰዊያ ሆኖ ስለሚያገለግል ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በዕብ.13:10 ላይ "መሠዊያ አለን" ያለው ታቦቱን እንደሆነ   ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጉሞታል። "ታቦት ነበረን" አላለምና ታቦት አለን ያለው በዘመነ ሐዲስ በመሆኑ መሠዊያ በሐዲስ ኪዳን ለመኖሩ ያስረዳል ብሏል... ከዚህ አንጻር የታቦቱ አገልግሎት ለመሠዊያ ነው። መሠዊያ አለን እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ያለ መሠዊያ የምትኖር ቤተ ክርስቲያን የለችም።
[ሁለቱ ኪዳናት ገጽ.310-311፤ መሪጌታ ሐየሎምና ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ]

👉 ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ እህት አብያተ ክርስቲያናት (Oriental Churches) ታቦት የተለመደ ህግ ነው፡፡ ስጋ ወደሙን የሚፈትቱት በታቦቱ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ፦ ግብፃውያን ታቦቱን "ሉህ" ይሉታል፡፡ ጽላት ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ ያለሱ ስጋ ወደሙ አይፈተትም፡፡ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት "የግሪክ፣ የሩሲያ የሩማንያና" የሌሎችም ወደ ክርስትና የተመለሱት ከአረማዊነት ስለሆነ የታቦትን ምስጢር አያውቁም፡፡ በታቦቱ ፈንታ ከመንበር የማይነሳ እንደ ታቦት የሚከበር የጌታ የስቅለቱ ወይም የግንዘቱ ስዕል ያለበት የነጭ ሐር መጎናጸፊያ አላቸው፡፡ ያለሱ ስጋውን ደሙን አይፈትቱም፡፡ ይህን በጽርዕ "አንዲሚንሲዮን" ይሉታል፡፡ "ህየንተ ታቦት" ማለት ነው፡፡ የሮማ ካቶሊኮች "ሜንሳ " "MENSA" ይሉታል፡፡ ጠረጴዛ ማለት ነው፡፡ [የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፡ አባ ጎርጎርዮስ ገጽ108-110]

👉 ስለዚህም የክርስቶስ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ስለሆነ ክብርና ስግደት ይገባዋል። ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጻፈበት ስለሆነ ስለ ስሙ ስግደት ለማቅረብ በታቦት ፊት እንሰግዳለን። ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች በላከው መልዕክቱ  "፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።" ፊልጵ.2:10-11 እንዳለ በታቦቱ ፊት እንሰግዳለን።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]



tg-me.com/mnenteyiklo/2822
Create:
Last Update:

ጥያቄ:- ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት ነው? ለምን  ይሰገዳል?

መልስ

ታቦት በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በምህረት በሚገለጥበት ጊዜ ዙፋኑ ነው፡፡  ከክርስትና በፊት የብሉይ ኪዳን አገር የነበረችው ኢትዮጵያ በክርስትና ጊዜም ከብሉይ ኪዳንም ያገኘቻቸውን ጠቃሚ ነገሮች በክርስትና መንፈስ እየተረጎመች ትጠቀምባቸዋለች፡፡
ከብሉይ ኪዳን የወሰደቻቸው አንዱ ጽላተ ኪዳን ታቦተ ህጉ ነው፡፡ የደብተራ ኦሪት ጽላት እግዚአብሔር በደመና ተከናንቦ ሙሴንና አሮንን የሚነጋግርበት ለእስራኤል ልጆችም በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ታቦት ግን የአምላክ ስጋና ደም የሚፈተትበት ስጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ህይወት አለው፡፡ ስጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን ሁሉ የሚጠራበት የምህረት ምስዋዕ ነው፡፡ ክብርና ሰግደትም ለዚህ ይደረግለታል፡፡

👉 በርግጥ የሐዲስ ኪዳን ታቦት ከብሉይ ኪዳን ታቦት የሚለይበት መንገድ አለው። በሐዲስ ኪዳን ታቦት የሚባለው የብሉይን ታቦትና ጽላት አንድ አድርጎ የያዘ ይመስላል። በብሉይ ጽላት ላይ  የተጻፉት ቃላትም አልተጻፉበትም። ምክንያቱም በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ቀዳማዊ እንደተገለጸው ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ የሚችል ጻሕልና ጽዋ የሚያስቀምጥ እንዲሆን ተወስኗል። በላዩም አልፋ ወኦ፤ ቤጣ ፤ የውጣ የሚባሉ አስማተ መለኮት (የአምላክ ስሞች) በአራቱ ማዕዘን ይቀረጽበታል። በመካከል ሥነ ስቅለት ይቀረጽበታል። "ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ታቦተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ተብሎ ይጻፍበታል። ኪሩቤል መንበረ ጸባዖትን እንደተሸከሙ ይሳልበታል። ከዚያም የቅዱሱ ስም ይቀረጽበታል። እስከ 15ኛው ምእተ ዓመት ከላይ ቅድስት ሥላሴ
ዝቅ ብሎ እመቤታችን ወደ ላይ አንገቷን በማቅናት ከታች ደግሞ ቅዱሱን ወደ እመቤታችን አቅንተው ይቀረጹ ነበር። ከላይ ታቦቱ ጻሕል ጽዋ እንዲያስቀምጥ ሆኖ የሚሰራው መሰዊያ ሆኖ ስለሚያገለግል ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በዕብ.13:10 ላይ "መሠዊያ አለን" ያለው ታቦቱን እንደሆነ   ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጉሞታል። "ታቦት ነበረን" አላለምና ታቦት አለን ያለው በዘመነ ሐዲስ በመሆኑ መሠዊያ በሐዲስ ኪዳን ለመኖሩ ያስረዳል ብሏል... ከዚህ አንጻር የታቦቱ አገልግሎት ለመሠዊያ ነው። መሠዊያ አለን እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ያለ መሠዊያ የምትኖር ቤተ ክርስቲያን የለችም።
[ሁለቱ ኪዳናት ገጽ.310-311፤ መሪጌታ ሐየሎምና ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ]

👉 ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ እህት አብያተ ክርስቲያናት (Oriental Churches) ታቦት የተለመደ ህግ ነው፡፡ ስጋ ወደሙን የሚፈትቱት በታቦቱ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ፦ ግብፃውያን ታቦቱን "ሉህ" ይሉታል፡፡ ጽላት ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ ያለሱ ስጋ ወደሙ አይፈተትም፡፡ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት "የግሪክ፣ የሩሲያ የሩማንያና" የሌሎችም ወደ ክርስትና የተመለሱት ከአረማዊነት ስለሆነ የታቦትን ምስጢር አያውቁም፡፡ በታቦቱ ፈንታ ከመንበር የማይነሳ እንደ ታቦት የሚከበር የጌታ የስቅለቱ ወይም የግንዘቱ ስዕል ያለበት የነጭ ሐር መጎናጸፊያ አላቸው፡፡ ያለሱ ስጋውን ደሙን አይፈትቱም፡፡ ይህን በጽርዕ "አንዲሚንሲዮን" ይሉታል፡፡ "ህየንተ ታቦት" ማለት ነው፡፡ የሮማ ካቶሊኮች "ሜንሳ " "MENSA" ይሉታል፡፡ ጠረጴዛ ማለት ነው፡፡ [የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፡ አባ ጎርጎርዮስ ገጽ108-110]

👉 ስለዚህም የክርስቶስ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ስለሆነ ክብርና ስግደት ይገባዋል። ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጻፈበት ስለሆነ ስለ ስሙ ስግደት ለማቅረብ በታቦት ፊት እንሰግዳለን። ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች በላከው መልዕክቱ  "፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥፤ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።" ፊልጵ.2:10-11 እንዳለ በታቦቱ ፊት እንሰግዳለን።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

BY ምን እንጠይቅሎ?


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2822

View MORE
Open in Telegram


ምን እንጠይቅሎ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

If riding a bucking bronco is your idea of fun, you’re going to love what the stock market has in store. Consider this past week’s ride a preview.The week’s action didn’t look like much, if you didn’t know better. The Dow Jones Industrial Average rose 213.12 points or 0.6%, while the S&P 500 advanced 0.5%, and the Nasdaq Composite ended little changed.

Look for Channels Online

You guessed it – the internet is your friend. A good place to start looking for Telegram channels is Reddit. This is one of the biggest sites on the internet, with millions of communities, including those from Telegram.Then, you can search one of the many dedicated websites for Telegram channel searching. One of them is telegram-group.com. This website has many categories and a really simple user interface. Another great site is telegram channels.me. It has even more channels than the previous one, and an even better user experience.These are just some of the many available websites. You can look them up online if you’re not satisfied with these two. All of these sites list only public channels. If you want to join a private channel, you’ll have to ask one of its members to invite you.

ምን እንጠይቅሎ from id


Telegram ምን እንጠይቅሎ?
FROM USA